Embelem of Federal Democratic Republic of Ethiopia Official Portal of Ministry of Finance and Economic Development  
Home Home Citizens Citizens Government Government Business Business Donors Donors Decrease font Increase font

 ተጠሪ መስሪያ ቤቶች

 ዓመታዊ መረጃ

 

የ1998 የበጀት አመት የመጀመሪያዎቹ ዘጠኝ ወራት ማክሮ ኢኮኖሚ ልማት ሪፖርት የዘጠኝ ወሩን የማክሮ ኢኮኖሚክ አካሎችን የልማት ሂደት ዋና ዋናዎቹን ባጭሩ ያስቀምጣል፡፡

 

ከመጋቢት 1998 ጀምሮ የአገሪቱ የአጠቃላይ ደረጃ የሸማቾች ዋጋ ኢንዴክስ በ12 ወር ተንቀሳቃሽ አማካይ መሰረት ሲሰላ 12% ነበር፡፡ ይህም ከባለፈው አመት የዋጋ ግሽበት 140% የሚያህል ነጥብ ጨምሯል፡፡ በየቀኑ በባንኮች መሀል ያለው የውጭ ምንዛሪ ግብይት በሶስተኛ ሩብ አመት ላይ ከብር ወደ ዶላር የውጭ ምንዛሬ ተመን በ0.34% ቀንሷል፡፡

 

በ1998 የበጀት አመት የመጀመሪያዎቹ ዘጠኝ ወራት ላይ የፌደራል መንግስቱ ገቢና የበጀት እርዳታን አንድ ላይ 10860.0 ሚሊዮን ብር ደርሶ ነበር፡፡ ይህም ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር በ623.8 ሚሊዮን ብር ወይም በ5.4% ቀንሷል፡፡
 

በዛው የአመት ጊዜ ላይ 2404.13 ሚሊዮን የሚሆን የውጭ ብድር ለተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች ተከፋፍሏል፡፡ 370.6 ሚሊዮን ብር የሚሆን አጠቃላይ የብድር አገልግሎቶች የውጭ ብድሮችን ለመጨረስ ተከፍሏል፡፡