የ1998 የበጀት አመት የመጀመሪያዎቹ ዘጠኝ ወራት ማክሮ ኢኮኖሚ ልማት ሪፖርት የዘጠኝ ወሩን የማክሮ ኢኮኖሚክ አካሎችን የልማት ሂደት ዋና ዋናዎቹን ባጭሩ ያስቀምጣል፡፡
ከመጋቢት 1998 ጀምሮ የአገሪቱ የአጠቃላይ ደረጃ የሸማቾች ዋጋ ኢንዴክስ በ12 ወር ተንቀሳቃሽ አማካይ መሰረት ሲሰላ 12% ነበር፡፡ ይህም ከባለፈው አመት የዋጋ ግሽበት 140% የሚያህል ነጥብ ጨምሯል፡፡ በየቀኑ በባንኮች መሀል ያለው የውጭ ምንዛሪ ግብይት በሶስተኛ ሩብ አመት ላይ ከብር ወደ ዶላር የውጭ ምንዛሬ ተመን በ0.34% ቀንሷል፡፡
በ1998 የበጀት አመት የመጀመሪያዎቹ ዘጠኝ ወራት ላይ የፌደራል መንግስቱ ገቢና የበጀት እርዳታን አንድ ላይ 10860.0 ሚሊዮን ብር ደርሶ ነበር፡፡ ይህም ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር በ623.8 ሚሊዮን ብር ወይም በ5.4% ቀንሷል፡፡
በዛው የአመት ጊዜ ላይ 2404.13 ሚሊዮን የሚሆን የውጭ ብድር ለተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች ተከፋፍሏል፡፡ 370.6 ሚሊዮን ብር የሚሆን አጠቃላይ የብድር አገልግሎቶች የውጭ ብድሮችን ለመጨረስ ተከፍሏል፡፡