የኢትዮጵያ ካርታ ሥራዎች ኤጀንሲ በመጀመሪያ በ1946 ዓ.ም እንደ አንድ ክፍል ተዋቅሮ በወቅቱ ለትምህርት ሚኒስቴር መስሪያ ቤት በተለያየ ደረጃ ለትምህርት መርጃ የሚያስፈልጉ ካርታዎችን ሲያዘጋጅ ቆይቷል፡፡ ከዛም በመቀጠል በብሄራዊ ደረጃ ያለው የካርታ ስራ ፍላጎት እየጨመረ በመምጣቱ የድርጅቱን አወቃቀር መቀየር አስፈላጊ ሆንዋል፡ በዚሁም መሰረት ድርጅቱ የካርታና ስነ-ምድር ኢኒስቲቲዩት በመባል ሲጠራ ቆይቷል፡፡ በመጨረሻም በአዋጅ ቁጥር 193/1972 ተቋቁሞ አሁን ያለውን አደረጃጀት ይዟል፡፡