ለአቶ ማሞ ምህረቱ ሽኝት ተደርገላቸው

Published: Sept. 4, 2025

ዛሬ ነሐሴ 29/2017 ዓ/ም. በገንዘብ ሚንስቴር ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በተገኙበት የማክሮ ኢኮኖሚ ኮሚቴው ለብሔራዊ ባንክ ገዥ ለነበሩት አቶ ማሞ ምህረቱ የሰንብት ሥነ ሥርዓት አካሂዷል፡፡

በዚህ ልዩ ፕሮግራም አቶ ማሞ በተለይም መንግስት በቅርብ ግዚያት የወሰዳቸውን ታሪካዊና ውጤታማ የኢኮኖሚ ሪፎርም ላይ በብሔራዊ ባንክ ገዥነትና የማክሮ ኢኮኖሚ ኮሚቴ አባልነት ላበረከቱት አስተዋፅኦ ከክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ምስጋና አቅርበው በቀጣይ በአለም ዓቀፍ ደረጃ ለሚጠብቃቸው የስራ ኃላፊነት በብቃት እንደሚወጡ በመተማመን መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል፡፡

256 Views