በሰው ኃብት ልማት ትግበራ አፈፃፀም እና በፕሮግራሙ የ2018 በጀት አመት ዕቅድ ላይ ከፌዴራል እና ከክልሎች ባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድርክ ተጀመረ፡፡
June 30, 2025
ሰኔ 23/2017 ዓ.ም - የኢትዮጵያ መንግስት በተመረጡ 42 ወረዳዎች ተግባራዊ በሚያደርገው የሰው ኃብት ልማት ትግበራ አፈፃፀም እና በፕሮግራሙ የ2018 ዓመታዊ የስራ ዕቅድ ላይ ከፌዴራል እና ከክልሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በአዳማ ከተማ የምክክር መድርክ ተጀመረ፡፡
የገንዘብ ሚኒስቴር የቻናል አንድ ፕሮግራሞች ማሰተባበሪያ መምሪያ ኃላፊ አቶ ደጉ ላቀው እንደገለጹት የምክክር መደረኩ ዋነኛ ዓላማ በተለይም የሰው ሃብት ልማት ፕሮግራም የሚተገብሩ ወረዳዎች የፋይናንስ ቢሮ ሀላፊዎችና ባለሙያዎች ስለ ፕሮግራሙ ዓላማ እና አተገባበር እንዲሁም ስለ ፕሮግራሙ ፋይናንስ ፍሰት በቂ ግንዛቤ እንዲያገኙ ማስቻል መሆኑን ተቅሰው የወረዳ ፈጻሚ አካላት የፕሮግራሙን ትግበራ በማሳለጥ ሂደት የሚጠበቅባቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ አሳስበዋል።
የሃገራችን የልማት እድገት የሚወሰነው ለሰው ሀብት ልማት በምንሰጠው ትኩረት በመሆኑ መንግስት ይህን የሰው ሀብት ልማት ትግበራ ፕሮግራም ቀርጾ ተግባራዊ በማድግ ላይ እንደሚገኝም አቶ ደጉ ላቀው ጨምረው ገልፀዋል።
የፕሮግራሙ ዓላማ በሁሉም ክልሎች የሚመለከታቸው የሰው ኃብት ልማት ትግበራ ዘርፎች የተቀናጀ ዕቅድና በጀት በማዘጋጀት ዕድሜያቸው 10 ዓመት የሞላቸው ሕጻናት ተማሪዎችን የመማር ውጤታማነትን ማሻሻል እና ዕድሜያቸው ከአምስት ዓመት በታች ለሆኑ ሴቶችና ወንዶች የስርዓተ ምግብ አቅርቦትና አገልግሎት በማሻሻል የሕጻናት መቀንጨር መቀነስ መሆኑም ተመልከቷል፡፡
በምክክር መድረኩ ከሁሉም ክልሎች የትምህርት፣ የጤና፣ የግብርና እንዲሁም የውሃ ልማት ቢሮዎች የተውጣጡ ከ500 በላይ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል፡፡