የኦዲት ግኝት የተመዘገበባቸው 39 የፌዴራል ባለበጀት መስሪያ ቤቶች በገንዘብ እንዲቀጡና ከባድ የጽሁፍ የማሰጠንቀቂያ ደብዳቤ እንዲጻፍባቸው ተወሰነ

April 20, 2022

ሚያዝያ 12 / 2014 . - በዋና ኦዲተር ባለፉት ሶስት አመታት ተመርምረው የኦዲት ግኝት የተመዘገበባቸው 9 የፌዴራል ባለበጀት መስሪያ ቤቶች የበላይ ሀላፊዎችና የፋይናንስ ዳይሬክተሮች እያንዳንዳቸው በቅደም ተከተል 10 እና 9 ብር እንዲቀጡ የተወሰነባቸው ሲሆን በሌሎች 30 ባለበጀት መስሪያ ቤቶች ላይ ደግሞ ከባድ የጽኁፍ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ እንዲጻፍባቸው ተወስኖ ተግባራዊ ተደርጓል፡፡

የገንዘብ ቅጣቱ የተወሰነባቸው የአሶሳ፣ የቡሌ ሆራ፣ የደብረማርቆስ፣ የኦዳ ቡልቱ፣ የባህር ዳር፣ የሲቪል ሰርቪስ፣ የድሬዳዋ ዩኒቨርስቲዎች ፕሬዚዳንቶችና የፋይናንስ ዳይሬክተሮች ሲሆኑ የብሔራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽንና የኢትዮጵያ ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት የበላይ ሀላፊዎችና የፋይናንስ ዳይሬክተሮችም የገንዘብ ቅጣቱ ከተወሰነባቸው ተቋማት መካከል ይገኙበታል፡፡

2010 እስከ 2012 . ባሉት ሶስት አመታት ውስጥ ሂሳባቸው የጎላ ችግር ያለበት በመሆኑ ተቀባይነት የሚያሳጣ አስተየያት የተሰጣቸውና ሂሳባቸውን አይቶ አስተያየት መስጠት ያልተቻለበት የእነዚህ 39 የፌዴራል ባለበጀት መስሪያ ቤቶች ሀላፊዎችና ተቋማት ላይ እርምጃ የተወሰደውየፋይናንስ ኃላፊነትን በአግባቡ ባለመወጣት የሚወሰዱ አስተዳደራዊ እርምጃዎች መመሪያ ቁጥር 48/2009›› መሰረት ነው፡፡

በዚህ መመሪያ አንቀጽ 15.1 መሰረት በማንኛውም የመንግስት መስሪያ ቤት የተሾመ ወይም የተመደበ ሰው በመንግስት የፋይናንስ አስተዳደር አዋጅ፤ በአዋጁ መሰረት በወጡት ደንቦችና መመሪያዎች መሰረት በህግ የተወሰነውን ሀላፊነትን ባለመወጣቱ ምክንያት በዚህ መመሪያ ከሶስት ጊዜ በላይ ቅጣት ከተጣለበት ከሀላፊነት እንዲነሳ ሊደረግ እንደሚችል ተደንግጓል፡፡

የገንዘብ ቅጣት ከተላለፈባቸው ዘጠኝ የፌዴራል ባለበጀት መስሪያ ቤቶች የበላይ ሀላፊዎችና የፋይናንስ ዳይሬክተሮች ውስጥ ሰባቱ የዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንቶችና የፋይናነስ ዳይሬክተሮች ሲሆኑ ሁለቱ ደግሞ የሌላ ባለበጀት መስሪያ ቤቶች የበላይ ሀላፊዎችና የፋይናንስ ዳይሬክተሮች መሆናቸው ታውቋል፡፡

1683 Views