የገንዘብ ሚኒሰቴር ለሰራተኞቹ ልጆች ያዘጋጀውን ሕፃናት ማቆያ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በይፋ አስመርቋል፡፡ የህፃናት ማቆያው ከ4 ወር- 3 ዓመት ዕድሜ ክልል ውስጥ ላሉ ልጆች አገልግሎት ይሰጣል፡፡
በገንዘብ ሚኒስትር ክቡር አቶ አህመድ ሺዴ የተመራው የኢትዮጵያ የልኡካን ቡድን ከሳውዲ አረቢያ የንጉስ ሰልማን የሰብአዊ እርዳታ ማእከል የበላይ ሀላፊ ከክቡር ዶ/ር አብዱላህ አልራቢሀ ጋር በሁለቱ ሀገራት የጋራ ሰብአዊና የእርዳታ ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡
ሁሉም ኢትዮጵያዊ ኢትዮጵያ ለተሰኘች ውብ ፕሮጀክት እውን መሆን በጋራ መቆም አንደሚገባውና ለልጆቻችን የተሸለች ኢትዮጵያን ማውረስ እንደሚጠበቅብን የገንዘብ ሚኒስቴር የፖሊሲ ጉዳዮች ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር እዮብ ተካለኝ ገለጹ፡፡
Copyright © 2021 MOF All Right Reserved